Saturday, December 16, 2017




የ አዲስ ነገር  ልዩ ጥንቅር...
በያዝነው የፈረንጆች ዓመት መጨረሻ ይፀድቃል ተብሎ የሚጠበቀው አከራካሪው የአሜሪካ የታክስ ማሻሻያ ሁለቱን አውራ ፓርቲዎች ለሁለት ከፍሎ ሲያነታርክ ቆይቶ  እነሆ በሪፐብሊካኖች አሸናፊነት 51 49 ድምፅ የአሜሪካ ኮንግረስ ህጉን አፅድቆታል፡፡
ማሻሻያው ህግ ሆኖ ለመውጣት አንድ እርከን ቢቀረውም የሚቀየር ነገር ግን እምብዛም ሊኖር አይችልም እየተባለ ነው፤
ትራምፕ በትዊተር ድረ ገፃቸው በታክስ አከፋፈሉ ላይ ጥቂት ለውጥ በማምጣት እና ትንሽ አሀዝን በመቀየር መካከለኛ እና ከፍተኛ ገቢ ያላቸውን ሰዎች ተጨማሪ ገንዘብ እንዲያገኙ እናደርጋለን፤ ባለሃብቶችም ብዙ ሰራተኞችን ይቀጥራሉ ብለዋል፡፡
ትራምፕ እንዲህ ቢሉም ገለልተኛ ነው የሚባለው የኮንግረስ በጀት ጽህፈት ቤት የሚባለው ተቋም ባወጣው ሪፖርት እቅዱ ደሀውን የበለጠ ሲያደኸይ ለባለፀጋው ደግሞ ሀብት ይጨምርለታል ብሏል፡፡
ሪፖርቱ እንደሚለው አመታዊ ገቢያቸው 30ሺህ ዶላር በታች የሆኑ አሜሪካውያን የበለጠ ሲጎዱ በዓመት 100 ሺህ ዶላር በላይ የሚያገኙ ደግሞ የበለጠ ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡
በዚህ ረቂቅ እቅድ የዜጎችን ማንነት እየለየ ይተገበር የነበረውን የታክስ ቅነሳ አካሄድ ውድቅ ያደረገ ሲሆን ብዙ የክሬዲት አይነቶችንም አስወግዷል፡፡
እንደውም የታክስ ቅነሳ የሚደረገው በበጎ ምግባር ለተሰማሩ ወገኖች ሲሆን ይህም ቢሆን ሐብታሙን የሚጠቅም ነው እየተባለ ነው፡፡ ሌላው ለሐብታሞች የተፈቀደው ነገር ደግሞ 20 በመቶ የታክስ ቅናሽ ነው ተብሏል፡፡
Visit our facebook page: www.facebook.com/ebsnewsroom

የ አዲስ ነገር ተጨማሪ ማስታወሻ!

ይህ ቃለምልልስ የተካሄደው በ ዲሴምበር 1 ቀን  ሪፐብሊካን የሴኔት አባላት ካደረጉት ስብሰባ በኋላ በወጣ መረጃ ላይ ተንተርሶ ሲሆን ከተወሰኑ ማሻሻያዎች ጋር የፊታችን ማክሰኞ ዲሴምበር 20/2017  በፕሬዝደንት ትራምፕ ፊርማ የሃገሪቱ ህግ ሆኖ ይፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል፤ እኛም ይህንኑ የአዲሱን የአሜሪካ የታክስ ህግን በሁለቱ አውራ ፓርቲዎች ድርድር የተደረጉ ማስተካካያዎች ና  በፕሬዝደንቱ ፊርማ የፀደቀውን ቋሚ የታክስ ሰነድ በመያዝ ተመልሰን መረጃዎችን የምናቀብ መሆኑን እንገልፅላችኋለን።        






Thursday, November 9, 2017

የ አዲስ ነገር  ልዩ ጥንቅር... በያዝነው የፈረንጆች ዓመት መጨረሻ ይፀድቃል ተብሎ የሚጠበቀው አከራካሪው የአሜሪካ የታክስ ማሻሻያ ሁለቱን አውራ ፓርቲዎች ለሁለት ከፍሎ ሲያነታርክ ቆ...