Friday, September 1, 2017

የዚምባብዌው ፕሬዝዳንት ሮቦርት ሙጋቤ ለሀገራቸው ፖሊሶች እባካችሁ ከአሽከርካሪዎች የምትቀበሉት ገንዘብ ይብቃ በማለት ወቅሰዋል

       


         
በሀገሪቱ ትላልቅ አውራ ጎዳናዎች ላይ ተመድበው የሚሰሩ ፖሊሶች መንገዱን በግዑዝ አካል እየዘጉ እና ለመክፈት ብር እየተቀበሉ እንደሆነ መረጃው አለኝ ብለዋል፡፡
እነዚህ መንገዶች የውጭ ሀገር ዜጎችን ማመላለሻ መስመሮች ናቸውና እባካችሁ ስማችን ዳግም ጥላሸት እንዲቀባ አታድርጉት  ብለው ተማጽነዋል፡፡

የዙምባቡዌ ፖሊሶች ለእርዳታ ሄደው ገንዘብ ተቀብለው  የሚመጡ ናቸው  ተብሎ ለብዙ አመታት የሙሰኝነታቸው ደረጃ ከፍ የሚያደርጉ ትችቶች  ደርሰውባቸው ያውቃሉ፡፡አሁን ደግሞ ብሶበት መታየቱን ሙጋቤ በአንደበታቸው መስክረዋል ሲል ዩናይትድ ፕረስ ኢንተርናሽናል ዘግቧል፡፡
ከዚህ በኋላ ተመሳሳይ ወንጀል እንዳይፈጸም ከተፈለገ ለህዝቡ ትራንስፖርት የሚሰጡ ወገኖች ማህበር ፈጥረው በጋራ በመንቀሳቀስ ሙሰኞችን ማጋለጡ ተገቢ ይሆናል በማለት ሙጋቤ ሰሚ ካለ ብለው መክረዋል፡፡

የ አዲስ ነገር  ልዩ ጥንቅር... በያዝነው የፈረንጆች ዓመት መጨረሻ ይፀድቃል ተብሎ የሚጠበቀው አከራካሪው የአሜሪካ የታክስ ማሻሻያ ሁለቱን አውራ ፓርቲዎች ለሁለት ከፍሎ ሲያነታርክ ቆ...