
የአውሮፓ ህብረት ይህን ውሳኔ ያሳለፈው ምግባና መጠጥ ለሁሉም ዜጎች በእኩል መጠን ማቅረብ ባልችልም መረጃዎችን መመገብ ግን አያቅተኝም ብሎ መሆኑን አሳውቋል፡፡ ይህነ የበጎ አድርጎት የገመድ አልባ ኢንተርኔት ፕሮግራም በ6000 ቦታዎች ላይ ለመጀመር ዕቅድ ወጥቶ ባለሙያዎች ለስራው እየተፈለጉ እደሆነም ተነግሯል፡፡ የትኛውም ለህዝብ እስራለሁ የሚል ተቋም ቅድሚያ መጠየቂያ ደብዳቤ ካስገባ ያለ ምንም ክፍያ በህንፃው አሊያም በጊቢው ውስጥ ተተክሎለት አላፊው አግዳሚው እንዲጠቀምበት ያደርጋል ብሎ የአውሮፓ ህብረት ቅስቀሳ በማደረግ ላይ መሆኑ ታውቋል፡፡ በዚህ የልግስና ፕሮግራም ውስጥ ትልቅ የፖለቲካ ጨዋታ መኖሩን ተመልክተናል የሚሉ የህብረቱ ፓለቲከኞች ነፃ የኢንተርኔት አገልግሎት አቅርበው ውሳኝ መረጃ ሊሰበስቡበት የታለመ አደገኛ ተግባር ነው በማለት የሚኮንኑትም አልጠፉም