
የሀገር ውስጥ በረራ የሚያካሂዱበትና የዓለማቀፍ አየር መንገዶች በአንድ ስም ተጠርተውና በአንድ ጠንካራ መሪ እየተዳደሩ ትርፋማ እንዲሆኑ ተወጥኗል፡፡ አየር መንገዶቹን ከማዋሃድ በተጨማሪም 25 በመቶ የሚሆነውን የድርጅቱ ድርሻ ለግል ባለሀብቶች በመሸጥ የገንዘብ መጠኑን ለማሳደግ ውጥን ላይ ናቸው፡፡
SOUTH AFRICAN AIRWAYS ARM MANGO እና SAA EXPRESS ሀገር በቀል አየር መንገዶች ናቸው ፡፡ ተጨፍልቀው አንድ ጠንካራ የትራንስፖርት ተቋም ለመመስረት የተዘጋጁት እነዚህ አየር መንገዶች የሀገር ውስጡን በረራና የዓለማቀፍን በጋራ በማመላለስ ትርፍ እንጂ ክስረት የሚለው ቃል ከድርጅቱ እንዲወጣ ይጥራሉ ያሉት PUBLIC ENTERPRICE MINISTER የሀገሪቱ ላይን ብራውን ናቸው፡፡