አፍሪካ ፋሽን ሪስፕሽን መቀመጫውን ፓሪስ ያደረገ የፋሽን ድርጅት ሲሆን ትርኢቱ ሲያቀርብ ይህ አራተኛ
ነው፡፡ የመጀመሪያዎቹ ሁለት ትርኢቶች በፓሪስ የተዘጋጀ ሲሆን የአፍሪካ
ፋሽን ለማስተዋወቅ እና ለማሳደግ የህብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ ቢዘጋጅ የተሻለ ነው በማለት ሶስተኛው እና አራተኛ
ዙር ትርኢቶች በአዲስ አበባ እንዲዘጋጅ መደረጉ ሰምተናል፡፡
በዚህ ዝግጅት ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ
ከ15 የሚበልጡ ዲዛይነሮች እና ሞዴሎች የተሳተፉ ሲሆን ዲዛይነሮቹ የሀገራቸውን ባህል ያሳያሉ ያሏቸውን ዘመናዊ ልብሶቻቸው አቅርበዋል፡፡
አገራችን ኢትዮጵያ በመወከል ወ/ሮ እጅጋየሁ ሃይለ
ጊዮርጊስ ከእጅ ጥበብ ስራዎቿን አቅርባ ነበር፡፡