Saturday, October 28, 2017
Monday, October 16, 2017
Sunday with EBS: እሁድን በኢቢኤስ - Hub of Africa /daily life / with Helen Be...
በእሁድን በኢቢኤስ በዚህ ዝግጅት # 2
- -የአፍሪካ ሐብ የፋሽን ሳምንት
- -ውሎ - የተዘዋዋሪ ሻይ ሻጭዋ ውሎ
- -ድምፃዊት ሄለን በርሄ በእሁድን በኢቢኤስ ስቱዲዮ ....መልካም ሰንበት!
Sunday with EBS: Special leza Award Coverage/ Cancer Awareness with Dr. ...
በእሁድን በኢቢኤስ በዚህ ዝግጅት #1
- የለዛ አዋርድ ልዩ ሪፖርት
የካንሰር በሽታ ግንዛቤ በዶ/ር ኤዶም
ኮሜዲያን ደረጀ ደስታ ጋብቻ ና የኢቢኤስ የጋብቻ ስጦታ
በእሁድን በኢቢኤስ ስቱዲዮ ....መልካም ሰንበት!
Friday, October 13, 2017
Thursday, October 12, 2017
What's New: Disability advocate Yetnebersh Nigussie receives 2017 'Alte...
ተቋሙ ላለፉት 37 ዓመታት በስራቸው የተመሰገኑ እና የተከበሩ እንዲሁም ነጥረው የወጡ ግለሰቦችን ሲሸልም ቆይቷል፡፡ በስቶኮልም ስዊዲን የሚገኘው Rights livelihood award foundation
ከዚህ በፊት ይህን ሽልማት ከኢትዮጵያ ካገኙት ፕሮፌሰር አክሊሉ ለማ እና ዶክተር ለገሰ በጥምረት ዶክተር መላኩ ወረደ እና ዶክተር ተወልደ ብርሃን ገ/እግዚአብሄር ናቸው፡፡ ከኢትዮጵያዊያን ሴቶች ደግሞ ወ/ሮ የትነበርሽ ንጉሴ ብቸኛ ተሸላሚ ናት፡፡
Tuesday, October 10, 2017
Monday, October 9, 2017
የውቅያኖስ ቆሻሻ ፅዳት
የአለምችን ውቅያኖሶች እጅግ በፕላስቲክ ቆሻሻዎች እየተሸፈኑ ነው ሲል ስጋቱን የገለፀው የአውሮፓ ኮሚሽን የድርሻዮን አበርክቼ ላፅዳ በማለት የ650 ሚሊዮን ዶለር በጀት አፅድቋል፡፡ ከየመኖሪያ አካባቢና ከመዝናኛ ስፍራዎች አንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ ውለው መሬት ላይ የሚጣሉት የፕላስቲክ ምርቶች ወደ ውቅያኖስ በውሃ ተወስደው እዛ ይገኛሉ ሲል ኮሚሽኑ በሳተላይት ያነሳውን ምስል አሳይቷል፡፡ እነዚህ የፕላስቲክ ቆሻሻዎች በየአመቱ ካልተሰበሰቡና ከውሃው ካልራቁ ከ30 አመታት በኋላ ህንድና አትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጣቸው ከሚይዙት አሳና ሌሎች ነፍሳት በበለጠ ፕላስቲክ ቆሻሻዎቹ ልቀው ይታይሉ የሚልም ስጋት አለው፡፡
Friday, October 6, 2017
Thursday, October 5, 2017
Tuesday, October 3, 2017
የ2019 የዲቪ ምዝገባ ሊጀመር ነው
ምዝገባው ከኦክቶበር 3 እስከ ኖቬምበር 7 የሚቀይ ሲሆን በዚህ
ፕሮግራም ከሁሉም የአለማችን ክፍሎች በአጠቃላይ 50000 አመልካቾች እንደሚቀበሉም ተገልጿል፡፡
የዲቪ አመልካቾች የመጀመርያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸው
ያጠናቀቁ እና የከፍተኛ ተቋም መግብያ ውጤት ያላቸው አልያም የዲግሪ ምሩቅ መሆን አለባቸው፡፡ የቴክኒክ እና ሞያ ስልጠና ግን እንደትምህርት
ማስረጃ እንደማያገለግል ኤምባሲው በላከው መግለጫ ገልጿል፡፡
አመልካቾች በድርጅቱ ድህረገፅ dvlottery.state.gov በመጠቀም ብቻ መመዝገብ የሚችሉ ሲሆን onetonline.org በመግባት ደግሞ
ለማመልከት ብቁ መሆናቸውን ማረጋገጥ ይችላሉ ተብሏል፡፡ አመልካቾች አንዴ ብቻ ማመልከት የሚችሉ ሲሆን በተደጋጋሚ ቅፁን መሙላት
ግን ከምዝገባው ውጪ እንደሚያደርጋቸው ተገልጿል፡፡ ለማመልከት ምንም አይነት ክፍያ የማይጠይቅ ሲሆን ኢምባሲው ክፍያ የሚጠየቀው
ለቃለ-መጠይቅ ያለፉ እድለኞችን ብቻ ነው ተብሏል፡፡
ለደህንነት ሲባል ኤምባሲው ለዲቪ እድለኞች ኢሜል የማይልክ ሲሆን
ከ ሜይ 1 2018 ጀምሮ አመልካቾች የተሰጣቸው የሚስጥር ቁጥር በመጠቀም ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡
የምስራቅ የደቡባዊ አፍሪካ የንግድና የልማት ባንክ /ቲዲቢ/ በኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቴን ከፍቻለሁ አለ፡፡
ከዚህ ቀደም
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ አውሮፕላኖችን ሲገዛ እንዲሁም አበሻ ሲሚንቶ ማሽኖችን ሲያስተክል የውጭ ምንዛሬ በብድር መልክ
ሰጥቻቸው የነበርኩት እኔ ነኝም ብሏል፡፡
አሁን በኢትዮጵያ ቅርንጫፉን የከፈተው ቲዲቢ የተሰኘው ባንክ ይህን ችግር ለመፍታት አማራጭ
ሆኖ የመጣ ሲሆን ከ40 የተለያዩ አለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ጋር በትብብር እንደሚሰራም ለማወቅ ችለናል፡፡ ከ20 በላይ በሆኑ
የአፍሪካ አገራት እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው እና ለተለያዩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ብድር በመስጠት የሚታወቀው ባንኩ አሁን ወደ 5 ቢሊዮን
ዶላር ገደማ ካፒታል እንዳለው ከባንኩ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል፡፡
በኢትዮጵያ እንደ ኢነርጂ እና ግብርና ባሉ ዘርፎች ላይ
የውጭ ምንዛሬ ብድር የመስጠት ፍላጎት እንዳለውም ነው የሰማነው፡፡
አፍሪካ ፋሽን ሪስፕሽን አዲስ አበባ ኤንድ ፓሪስ በሚል ርዕስ የፋሽን ትርኢት በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ ተካሄደ፡፡
አፍሪካ ፋሽን ሪስፕሽን መቀመጫውን ፓሪስ ያደረገ የፋሽን ድርጅት ሲሆን ትርኢቱ ሲያቀርብ ይህ አራተኛ
ነው፡፡ የመጀመሪያዎቹ ሁለት ትርኢቶች በፓሪስ የተዘጋጀ ሲሆን የአፍሪካ
ፋሽን ለማስተዋወቅ እና ለማሳደግ የህብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ ቢዘጋጅ የተሻለ ነው በማለት ሶስተኛው እና አራተኛ
ዙር ትርኢቶች በአዲስ አበባ እንዲዘጋጅ መደረጉ ሰምተናል፡፡
በዚህ ዝግጅት ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ
ከ15 የሚበልጡ ዲዛይነሮች እና ሞዴሎች የተሳተፉ ሲሆን ዲዛይነሮቹ የሀገራቸውን ባህል ያሳያሉ ያሏቸውን ዘመናዊ ልብሶቻቸው አቅርበዋል፡፡
አገራችን ኢትዮጵያ በመወከል ወ/ሮ እጅጋየሁ ሃይለ
ጊዮርጊስ ከእጅ ጥበብ ስራዎቿን አቅርባ ነበር፡፡
Subscribe to:
Posts (Atom)
የ አዲስ ነገር ልዩ ጥንቅር... በያዝነው የፈረንጆች ዓመት መጨረሻ ይፀድቃል ተብሎ የሚጠበቀው አከራካሪው የአሜሪካ የታክስ ማሻሻያ ሁለቱን አውራ ፓርቲዎች ለሁለት ከፍሎ ሲያነታርክ ቆ...